Ministry of Labor and Skills

የሥራና ክህሎት ሚንስቴር ከሃገር ውስጥ እና በሃገር ውጪ ያሉ የስራ ዕድሎችን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ባለው የሪፎርም ስራና በተዘረጋው ቴክኖሎጂ በአምስት ወራት(ወ.ሴ) ከ146,291 በላይ ዜጎች በውጭ ሃገር የስራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል።

ሚንስቴር መስሪያቤቱ በውጭ ሃገር የሰራተኛ ስምሪት የዜጎቻችን ደህንነት እና ጥቅም የሚያስጠብቅ እንዲሁም ብልሹ አሰራርን የሚከላከል ቴክኖሎጂ በውስጥ አቅም አልምቶ እጅግ ፈጣን የሆነ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

በመሆኑም ሚንስቴር መስሪያቤቱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በሚያከናውናቸው የሪፎርም ተግባራት እና በዘርፉ በሚሰጠው ፈጣን አገልግሎት እንዲሁም የስምሪት መደረሻዎችን ለማስፋት ከተለያዩ ሃገራት ጋር እየገባናቸው ያሉ አዳዲስ ስምምነቶች የሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይል ፍላጎት ያላቸው በመሆኑ በተዘረዘረው የሞያ መስክ ተመዝግበው ስልጠና ለመውሰድ ፍቃደኛ የሆናቹ ዜጎች በኢትዮጲያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት https://www.lmis.gov.et ድህረ-ገጽ ላይ ገብታቹ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን።

1. Driver – ሹፌር
2. Cleaner – የጽዳት ባለሞያ
3. Chef – በሼፍ
4. Laborer – በጉልበት ሰራተኝነት
5. Security Guard/ Security Officer – የጥበቃ ባለሞያ
6. Technician – ቴክኒሺያን
7. Carpenter – የእንጨት ባለሞያ
8. Store Keeper – የሱቅ ጠባቂ

ተመዝጋቢዎች ድህረ-ገጹ ላይ በሚደረገው ምዝገባ መረጃዎቻችሁን በትክክል የማስገባት ሃላፊነት ያለባችሁ ሲሆን መረጃዎቻችሁን አስገብታችሁ ስትጨርሱ ሲስተሙ በሚሰጠው የባዮሜትሪክስ ቁጥር አቅራቢያችሁ በሚገኙ አንድ ማዕከላት በመሄድ የባዮሜትሪክስ ምዝገባ በማደረግ ምዝገባችሁን እንድታጠናቅቁ እናስታውቃለን።

ማሳሰቢያ:

ለመመዝገብ የፓስፖርት ባለቤት መሆን የማያስፈልግ ሲሆን ፤ የባዮሜትሪክስ ምዝገባ የሚያከናውኑ አንድ ማዕከላትን ዝርዝር https://lmis.gov.et/ossc-lists ከዚህ ላይ ማግኘት ይቻላል።

የሥራዎ ባለቤት እርስዎ ኖዎት !